ምሥጢረ ጥምቀት
ይህ ከማይደገሙ ምሥጢራት ውስጥ ይመደባል።
- ጥምቀት ከሥላሴ መወለድ ነው
- ጥምቀት ወደ ማንኛውም ምሥጢር ለመግባት በር ነው
- ኃጢአትን የምታስተሰርይ ጥምቀት አንዲት ናት
በጥምቀት ሰው መንፈሳዊ ልደትን ዳግመኛ ይወለዳል እና መንፈሳዊ እድገትን ያስከትላል።
ሕዝ 36:-25 / ሮሜ 6:-3-4 / 1ኛ ቆሮ 6:11
Orthodox Teaching
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰባቱ ምስጢራት ለምእመናን የእግዚአብሔር ጸጋ የሚሰጥባቸው ቅዱሳን ምስጢራት ናቸው።
በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ ሥም በአንድ አምላክ ። አሜን።
“ሰባቱ ምሥጢራት” የሚለው ቃል በቁጥር ሰባት መሆናቸውን ያመለክታል። እነዚህ ለምእመናን የእግዚአብሔር ጸጋ የሚሰጥባቸው ቅዱሳን ምስጢራት ናቸው። በእነርሱ ተሳትፎ ሰው መንፈሳዊ ሕይወት፣ መፈወስ፣ ቅድስና እና ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረትን ያገኛል።
ምሳሌ 9:-1
“ምስጢራት” ተብለው የሚጠሩበት ምክንያቱ የመለኮታዊ ምስጢሮች በመሆናቸው ነው። በውጭ ሲታዩ በቤተ ክርስቲያን የሚፈጸሙ በሥጋዊው አይን የሚታዩ ሥርዓቶች ናቸው፤ በውስጣቸው ግን የማይታየውን የእግዚአብሔር ጸጋ ያሰጣሉ። ሰው ከእኚህ ምሥጢራት ካልተሳተፈ መንግስተ እግዚአብሔርን እንኳን መግባት ሊያይ አይችልም።
ዮሐንስ 3:-3 እና 5
እነዚህም አገልግሎቶች የሚፈጸሙት በእግዚአብሔር እንደራሴ በሆነው በካህኑ ቡራኬ እና ጸሎት አማካኝነት ነው። በጥንታውያን ቤተ ክርስቲያን ሁሉ የታወቁ፣ የታመነባቸው እና የሚሰራባቸውም እነዚህ ናቸው።
ይህ ከማይደገሙ ምሥጢራት ውስጥ ይመደባል።
በጥምቀት ሰው መንፈሳዊ ልደትን ዳግመኛ ይወለዳል እና መንፈሳዊ እድገትን ያስከትላል።
ሕዝ 36:-25 / ሮሜ 6:-3-4 / 1ኛ ቆሮ 6:11
ሜሮን ማለት ቅብአት ማለት ሲሆን ከጥምቀት ቀጥሎ ወዲያው የሚፈጸም ምስጢር ነው።
ዘጸአት 30:-22-30 / 1ኛ ሳሙ 10:-1 / 1ኛ ዮሐንስ 2:-20 እና 27
ቁርባን መቅረቢያ፣ መቀራረቢያ፣ መገናኛ ማለት ነው።
በአዲስ ኪዳን ምእመናን የሚያቀርቡት ሥጋ እና ደም በቀር ሌላ መስዋዕት የለም።
ዮሐን 6:-27 እና 53 / 1ኛ ቆሮን 11:-26 / ዕብራ 9:-14
ክህነት ማለት የአገልግሎት ማዕረግ ሲሆን በጳጳሳት አንብሮተ እድ የሚሰጥ ምስጢር ነው።
በዚህ ምስጢር ካህናት የማሰርና የመፍታት ሥልጣን፣ ሌሎች ምሥጢራትን የማከብር እና የማቀደስ ሥልጣን ይቀበላሉ።
ማቴዎ 16:-19 / ዮሐን 20:-23 / 1ኛ ጢሞቲ 4:-14
ንስሓ ማለት መጸጸት፣ መመለስ እና ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ማለት ነው።
በዚህ ምስጢር ምእመናን የኃጢአት ይቅርታን ያገኛሉ እና በጸጋ ይታደላሉ።
ምሳሌ 28:-13 / 1ኛ ዮሐን 1:-8-10 / ያዕቆብ 5:-16
ምሥጢረ ተክሊል በቤተ ክርስቲያን በካህን ጸሎት እና በረከት የሚፈጸም ቅዱስ ጋብቻ ነው።
በዚህ ምስጢር ወንድና ሴት በቅዱስ ጋብቻ ይጣመራሉ እግዚአብሔርም አንድ ያደርጋቸዋል።
ማቴ 19:-3-9 / ኤፌሶ 5:-28-31 / 1ኛ ቆሮንቶ 7:-2-4
ምሥጢረ ቀንዲል ለታመሙ በጸሎት እና በቅዱስ ቅብአት የሚሰጥ የፈውስ ምስጢር ነው።
በዚህ ምስጢር እግዚአብሔር ፈውስን እና መመለስን ይሰጣል።
ኢሳ 1:-6 / ሉቃስ 10:-34 / ማር 6:-13 / ያዕቆብ 5:-13-15
እንግዲህ መንፈሳዊ ህይወት በነዚህ በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ይመሠረታል በነዚህም ይጸናል። ስለዚህ እያንዳንዱ የሰው ልጅ በነዚህ በርነት እንዲገባ በነዚህ እንዲጸና ሁሉም የማወቅ፣ የማሳወቅ፣ የመፈጸም እና የማስፈጸም መንፈሳዊ ግዴታ አለበት።
2ኛ ጴጥሮስ 1:-10
የእግዚአብሔር ቸርነት የእናታችን የእመቤታችን አማላጅነት ከእኛ ጋር ለዘልዓለም ጸንቶ ይኑር ይቆየን።
Orthodox Teaching
In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the Seven Mysteries are holy sacraments through which the grace of God is given to the faithful.
In the name of the Father, and of the Son, and of the Holy Spirit, one God. Amen.
The expression “the Seven Mysteries” signifies that they are seven in number. These are the holy mysteries through which the grace of God is bestowed upon the faithful. By participation in them, man receives spiritual life, healing, holiness, and communion with God.
Proverbs 9:1
They are called “mysteries” because they are divine mysteries. Outwardly, they are rites performed in the Church and visible to the bodily eye; inwardly, however, they impart the invisible grace of God. Unless a man partakes of these mysteries, he cannot even see, much less enter, the Kingdom of God.
John 3:3 and 5
These sacred ministrations are performed through the blessing and prayer of the priest, who serves as the steward of God. These are the mysteries known, believed, and practiced in the ancient Church.
Baptism is numbered among the non-repeatable mysteries.
Through baptism, a man is born again into spiritual life and growth. He receives a spiritual father, heavenly nourishment through the Body and Blood of Christ, and a path toward the Kingdom of Heaven.
Ezekiel 36:25 / Romans 6:3–4 / 1 Corinthians 6:11
Chrismation follows immediately after baptism. It is not merely an anointing, but a seal that grants the grace of the Holy Spirit.
Exodus 30:22–30 / 1 Samuel 10:1 / 1 John 2:20, 27
Holy Communion is the sacrament through which believers unite with God.
This is the highest and complete sacrifice — the Body and Blood of Christ — through which believers receive life.
John 6:27, 53 / 1 Corinthians 11:26 / Hebrews 9:14
This mystery refers to priesthood and ministry.
Through ordination, priests receive authority to administer the mysteries, reconcile people with God, and serve the Church.
Matthew 16:19 / John 20:23 / 1 Timothy 4:14
Penance is repentance — turning back to God.
Through this mystery, believers receive forgiveness and restoration through God’s grace.
Proverbs 28:13 / 1 John 1:8–10 / James 5:16
Holy Matrimony is the sacred union of a man and a woman blessed in the Church.
Through this mystery, God unites them as one and grants grace for their life together.
Matthew 19:3–9 / Ephesians 5:28–31
Holy Unction is the mystery of healing through prayer and anointing.
Through this mystery, God grants healing and restoration.
Isaiah 1:6 / James 5:13–15
The spiritual life is founded upon these Seven Mysteries and strengthened through them. Every believer is called to know them, practice them, and grow through them in faith.
2 Peter 1:10
May the goodness of God and the intercession of Our Lady remain with us forever.